እንዲህም አላቸው። ክርስቶስ መከራ ይቀበላል በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ይነሣል፥ በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል።እናንተም ለዚህ ምስክሮች ናችሁ።እነሆም፥ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ።
(ሉቃ. 24:46-49). ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳ በኍላ መጀመሪያ ለመረጣቸው ሐዋሪያት የተናገራቸው በዚህ መልኩ ነበር።
ጌታ ኢየሱስ ከማረጉ በፊት ሊጠብቁት የሚገባ ተስፋ እንዳለ ሲነግራቸው ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ።
(ሐዋ 1:8).
"ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ የተሰጠ ሃይማኖት
(ይሁዳ 3) የተወለደው ሐዋሪያው ጴጥሮስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ በበአለ ሃምሳ ቀን በሰበከው ስብከት ነው።
(ሐዋ 2:14-47). ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የመንግስተ ሰማየት መክፈቻ ቁልፎች ሊሰጠው ቃል የገባለት ሐዋሪያው ጴጥሮስ እንደሆነ የሚታወቅ ነው።
(ማቴ. 16:15-19).ከዚህ በታች የተጠቀሱ ጥቅሶች የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋሪያት በዚህ እምነት ላይ የተሰጣቸውን ስልጣን ያሳያሉ።:
(ማቴ. 10:40; ሉቃ 10:16; ዮሐ 15:16; 17:18-20; ማር 16:15; ሉቃ. 24:44-45; ሐዋ 10:39-42; ገላ 1:8-12; 1 ቆሮ 3:10-11; 2ቆሮ. 4:3-4; I ዮሐ 4:6; I ዮሐ 1:1-4; ኤፌ 2:20; ራእ 21:14)የአለምአቀፍ ሐዋሪያዊት ቤተክርስቲያን ከዚህ በታች ጠቅለል ባለ መልኩ በቀረቡት የእምነት አንቀጾች የመጽሃፍ ቅዱስ ጸሃፊዎችን፣ነቢያትንና የሐዋሪያት ትምህርቶችንና ልምምዶች ታምናለች፤አጥብቃም ታስተምራለች።>